News
Get in Touch
English
The Ministry
Irrigation Development Sector
Projects
Lowland Development Sector
Administration sector
Publications
Search
News
Get in Touch
English
In
News
•
August 14, 2024
የኢፌዴሪ መስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በተከሰተ የመሬት ናዳ ለተጎዱ ወገኖች የ5 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አደረገ ****************************************** የኢፌዴሪ መስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር አብረሃም በላይ በጎፋ ዞን በተከሰተ የመሬት ናዳ ምክንያት በወገኖቻችን ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት በመድረሱ የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለፅ ፈጣሪ የሞቱትን ነፍሳቸውን እንዲምር ተመኝተዋል። ጉዳቱ የሁላችን የኢትዮጵያውያን መሆኑንም ሚኒስትሩ አብራርተዋል። የክልሉ መንግስትና የዞኑ አስተዳደር በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውንና ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉትን በቋሚነት ለማቋቋም እያደረገ ያለውን ጥረት ለመደገፍ የ5 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መደረጉን አመልክተው ድጋፉን ለዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አስረክበዋል። በቀጣይ ተጎጂዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚደረገው ተግባር እስኪጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ ለማድረግም ቃል ገብተዋል። የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ በበኩላቸው የኢፌዴሪ መስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር አብረሃም በላይ እና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እስከ ቦታው ድረስ በመሄድ በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሀዘን በመግለፅ የገንዘብ ድጋፍ በማድረጋቸው በዞኑ አስተዳደር እና በተጎጂዎች ስም አመስግነዋል። ተጎጂዎችን እና ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ሀብት የሚጠይቅ በመሆኑ ድጋፋቸው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ዋና አስተዳዳሪው ጠይቀዋል።
Privacy Preference Center
Privacy Preferences
This site is registered on
wpml.org
as a development site.